Sunday, May 31, 2009

"ቋንቋችንን እንጠብቅ"

በስመአብ ወወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።  በእግዚአብሄር ፈቃድ ይህችን ለማለት ወደድኩኝ ። ማንነት በሰብናችን ላይ የሚጫወተው ሚና የትዬለሌ ነው ። ስለ እኛነታችን ማንነታችን አፍ አውጥቶ ይናገራል ማንነት ለራሳችን ካለን አመለካከት በዋናነት ይመነጫል ስለ ራሳችን ያለን ያለን አመለካከት ደግሞ በከፍተኛነት ስለራሳችን ካለን ግንዛቤ እና ዕውቀት ይመነጫል። ስለዚህ ማንነት ማለት አንድ ሰው ከመጣበት ወይንም ከሚወለድበት ሀገር ፣ የዘር ሀረግ፣ ቤተሰብ ፣ ህብረተሰብ ፣ የሚወርሰውን እንደ ሐይማኖት ፣ሀገር ፣ባህል እና ቋንቋዎች ላሉ እሴቶች  ያለው አመለካከት የግለሰቡን ማንነት ይሰጡታል። ይንን አጠር ያለጽሁፍ ለማቅረብ መነሻ የሆነኝ እ.ኤ.አ 2004 በአቶ አማረ አፈለ  የተጻፈው ኢትዩጵያ የሰው ዘር የተገኘባት የእምነትና የሥልጣኔ ምንጭ ናት የሚለው መጽሃፋቸው ነው።

 እኔ ስለራሴ ያለኝ ግንዛቤ፣ ዕውቀት እና መረጃ የተሳሳተ እና የትምታታ ከሆነ ለራሴ ያለኝ እመለካከትም እንደዚሁ የተዛባ እና ዝቅያለ ይሆናል።እዚህ ላይ አንባቢዎቼ እንዲረዱልኝ የምፈልገው ነገር ስለራሳችን ስል በግል ሳይሆን በጋራ ስለምንጋራችው እሴቶች ማለቴ ነው።ለምሳሌ ሃይማኖት፣ ባህልን፣ ቋንቋን እና ሀገርን በዋናነት የሚመለከት መሆኑን እሳቤ ውስጥ እንዲገባልኝ አሳስባለሁ። አንድ ሰው ስለ ስለሃማኖቱ፣ ቋንቋው፣ ባህሉ እና ሃገሩ ያለው አመለካከት፣ግንዛቤ፣ መረጃ እና እውቀት የተሳሳተ እና የተንሸዋረረ ክሆነ  በግለሰብነት ደረጃ ስለራሱ ያለው  አስተሳሰብ እንደዛው የተምታታበት እና የተወላገደበት ይሆናል። ይባስ ብሎም በነጋ በጠባ የሚሸማቀቅበት  ይሆናል። በዚህ ብቻ አያበቃም ማንነት የሌለው ባይተዋርነት ስሜት በተደጋጋሚ  ይሰማዋል ይህ ደግሞ አደገኛ የሚሆንበት ጊዜ አለ ። ይህም ሐይማኖት፣ ቋንቋ ፣ባህል እንደ አሮጌና እንዳለፈባቸው በመቁጠር የራሳቸን ያልሆኑ ሀይማኖቶች፣ ቋንቋዎች፣ ባህሎች ላይ የሙጥኝ እንድንል ያደርገናል ።

በዚህ ብቻ ሳያበቃ በሃይማኖታችው፣ በባህላችው፣ ቋንቋቸው ላይ  የሚቃጣውን ንቀት፣ጥቃት፣ የሃሰት ወሬ፣ቧልት እና ውርደት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ግብረአበር በመሆን የድጊቱ ተሳታፊ ሲሆኑ ይስተዋላል። በርግጥ አንድ ሰው ማንነት አልባ መሆን ጮቤ የሚያስረግጣችው አካሎች እንዳሉ የማይታበል ሃቅ ነው ።በተለይ አሁን ባለንበት ዘመን አለም አንድ መንደር በሆነችበት (ግሎባይላዜሽን)  ሐይማኖት ባህል እና ቋንቋ እንደ ሸቀጥ በገንዘብ ሲቸበቸቡ እና ሲራገፉ ስናይ ይህ ማንነቱ ግራ የተጋባበት እና የተምታታበት የሰለጠነ መስሎም ስለሚሰማው ሐይማኖት፣ባህል፣ ቋንቋ እንደሌለው ብሩን አውጥቶ ሲሸምት መመልከት የሚፈጥረው ስሜት በደም ተቀላቅሎ አንጀት ያማስላል ።

አበው ነገር በምሳሌ ጥጅ በብርሌ እንዲሉ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን ጋር በተገናኘ አንድ ነገር ልበል ይህውም የቋንቋዎች አባት የሆነውን  ግዕዝን ይመለከታል ግዕዝ ረጅም ጊዜን ያስቆጠረ እድሜ አለው እንደውም ግዕዝ ከእግዚአብሄር በቀጥታ  የተሰጠን ቋንቋ መሆኑን እንናገራልን ።ግእዝ የእለት ተለት መነጋሪያነቱን እያጣ እና ተናጋሪዎቹም እያነሱ በመሄዳቸው በቤተክርስትያን ብቻ ተወስኖ ይገኛል።

ኢትዩጵያዊው በማንነቱን ፍለጋ በተባለ መጽሃፍ ገጽ 298 "ግእዝ ማለት መጀመሪያና መነሻ ራሱን የቻለና ነጻ ማለት ነው። በዕብራውያን ዕብራይስጥ ፣በአረብ አረቢኛ፣ በእንግሊዝ እንግሊዘኛ ፣እንደሚባለው ባገር ወይም በነገድ ወይም በተናጋሪው ህዝብ ሳይህን በራሱ የሚጠራ ፊደልና ሥርአቱ ራሱን ችሎና ተሟልቶ የተሰናዳ ቋንቋ ስለሆነ ግእዝ ተባለ። ይህ የቃሉ ትርጉም ግዕዝ የአዳም እና ሄዋን ቋንቋ ነበር" ሲሉ ጽፈዋል።

ግእዝ የአዳም እና የሄዋን እርስ በርሳቸው እና ከእግዚያብሔር የሚነጋሩበት ቋንቋ ነበር ይላል። ይህ ማለት እግዚአብሄር ከገነት ጀምሮ አዳም እና ሄዋንን ሲያናግርበት እንደቆየ ያሳየናል። ኦሪት ዘፍጥረት ምራፍ 11 ቁጥር 1 "ምድር ሁሉ በአንድ ቋንቋ ነበርች" ይላል።  ሌላው ግእዝ ክእግዚአብሄር በቀጥታ  የተሰጠን ቋንቋ ለመሆኑ ስለ መሆኑ አቶ አማረ አፈለ "ከታሪክ መጽሃፎች እንደምንረዳው የአዳም ቋንቋ ግእዝ ነበር የቀደሙ ምሁራን አብዛኛዎቹ የሚሉት የኢትዮጵያዊ ፊደል ነው" ሲሉ ጠቅሰዋል ። ፈለግ መጽሄት ጥቅምት 1985 ዓ.ም. ገጽ 39 "የኢትዩጵያ ፊደል ለምዕራቡ አለም መሰረት መሆኑ ተደረሰበት" ሲል ጽፏል። ታዲያ ይህ ሁሉ የሚያሳየው አሁን የምንጠቀምበት ፊደላችን ገዝተነው ወይም ከቀኝ ገዢዎች እንድንጠቀምበት የተሰጠን ሳይሆን ከፈጣሪያችን ከእግዚያብሔር የወረደልን ነው።

ነገር ግን ማንነታችንን አሳጥተው ትውልዳችንን በራሱ የማይተማመን ለሐሃይማኖቱን እና ለቤተክርስቲያኑ በእኔነት እና ተቆርቋሪነት ስሜት ይማይሰማው ትውልድ እንዲፈጠር አበክርው የሚሰሩ የውጭ መናፍቃን እንዳሉ በግልጽ እያየነው ነው። ይህ ብቻ ሳያንስ የነሱ የገደል ማሚቶዎች የሆኑት የውስጥ መናፍቃን  የእጅ አዙር ቀኝ ገዢዎች መሳሪያ በመሆን እነሱ የሚሏቸውን እንደ በቀቀን ሲያስተጋቡ ይስተዋላል። ግእዝ ከነፊደሉ አዳም እና ሔዋን ተስጥቶአችው በአባቶቻችን የህይወት መስዋትነት ተከፍሎበት ተጠብቆልን ይህው እኛ ልጆቻቸው እየተጠቀምንበት እንገኛልን።

ሆኖም ግን ሆን ብለው እኛን ለማሸማቀቅም እራሳችንን የበታች አድርገን እንድንጠላ እና የኔነው የምንለው ነገር እስክናጣ ድረስ ባገኙት አጋጣሚ ስለድህነታችን፣ረሃባችን፣ጎጠኝነታችን፣ሗላ ቀርነታችን፣ጦረኝነታችን ስለሚለፍፉት የረጅም እድሜ ቋንቋ ባለቤት መሆናችን እና አለም ላይ ላሉ ፊደሎች ሁሉ መነሻ አባት ፊደል እንዳለን ግን ለቀበሉት ቀርቶ ሲሰሙት እንኳን ኮሶ ጠጣ እንደተባለ ሰው ፊታቸውን ያጠቁሩታል እኛም ብንሆን ይህን የመሰለ የታሪክ ባለቤቶች ሆነን ሳለ የግድ ከባዕድ ጻህፍት እስኪነገረን ወይም እስኪጻፍልን ድረስ መጠበቅ የለብንም።

ሌላው ብከፍተኛ ሁኔታ አጽንዎት ሊሰጠው የሚገባ ነገር ልጆቻችን ይህንን ይመሰለ ለሌላም የተረፈ አባት ቋንቋ ባለቤት እና ተረካቢ መሆናቸውን ተረድተው ቋንቋቸውን እና ፊደላቸውን እንዲያውቁልን የተቻለንን ማድረግ ግድ ይለናል። ልጆቻችን በሰው ሀገር ሲኖሩ የራስ ቋንቋቸውን ባለማወቃቸው ማን እንደሆኑ ግራ እስቲገባቸው ድረስ እንዲሆኑ ተደርገዋል። የለም ኢትዩጵያዊ ነኝ እንዳይሉ ቋንቋውን፣ባህሉን፣በቅጡ አላወቁም እንዴትስ አድርገው እሴቶቻችንን ይረከቡን የለም ኢትዩጵያዊ አይደለንም እንዳይሉ "ኢትዩጵያዊ መልኩን ነብር ዥንጉርጉርነቱን አይለውጥም" የሚለው አምላካዊ ቃል በየሄዱበት የሚመለከታቸው ሁሉ ስማቸውን እንኳን ሳይጠይቅ ኢትዮጵያዊ ናችሁ እያለ ይጠይቃቸዋል ስለዚህ እነዚህ ተውልዶች ከየት ይሁኑ…? ታዲያ ለዚህ ምርጫ ለሌለው ጥያቄ መድሃኒቱ ልጆቻችንም ሆኑ እራሳችን የባህሪ ለውጥ በማምጣት እንከን ስለማይወጣለት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሐይማኖታችን፣ ስለቋንቋችን፣ፊደላችን እና ጨዋው ባህላችን መመለስ ይኖርብናል። ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ባለቅኔ (ሎሬት) ጸጋዬ ገብረ መድህን ጦቢያ ምጽሄት ቅጽ 5 ቁጥር 11 1990 ዓ.ም.  ገጽ 9 "አውሮፓውያን የ እስያ ቋንቋዎች (ግሪክ ላቲን ዕብራይስጥ ፅርዕ ዕረብ) እጀግ በጣም ብዙ የካም አበው ግሶችና ስሞች ዛሬም ተውርሰው የምናገኛችው። በኛ ባህል ላይ ተመሰርተው ነው ብስተኃላ የራሳችው ባህል የገነቡት። የፍልስፍናዎች  ሁሉ መሪ ፍልስፍና ራስህን እውቅ ነው። እኛ ግን ዛሬ ሆዳችንን እንጂ ራሳችን አናውቅም" ሲሉ ጽፈዋል።

ታዲያ አብዛኞቻችን የባዕድ ቋንቋ ባለማወቃችን ሲያሽማቅቀን እና የበታችነት ስሜት ሲያላብሰን ይስተዋላል ይህ ግን አግባብ አይደለም የሰው ሀገር ቋንቋ አለማወቅ ሀጢያት አይደለም በጭራሽ ሊያሸማቅቀን አይገባም በርግጥ ቋንቋን ማወቅ ጠቃሚነቱ አጠያያቂ ባይሆንም የራስ ቋንቋን እያፈሩበት፣እያንቋሸሹ እና እያጣጣሉ መሆን በጭራሽ የለበትም።

ሲሆን ሲሆን ከ እግዚአብሄር የተሰጠን አለም ሁሉ ከኛ ፊደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እየገለበጠ የሚጠቅምበት የፊልዶች አባት ቋንቋ ባለቤቶች የሆንን ቀና ብለን መሄድ እና ኮርተን ሌላውን ማስተማር ነበር የሚገባን።

ማጠቃለያ ታዲያ ይችህ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን ከፈጣሪያችን ጋር የምታገኛኝን ብቻ ሳትሆን ጠቅላላ ማንነታችን ፣የታሪካችን፣ባህላችን፣ቋንቋችን እና የስልጣኔያችን መገኛ ምንጭ ናት። መንግስት ሆና ላለፉት ሺህ አመታት ሀገራችንን አስተዳድራለች ይህን ተከትሎ ስለ መንግስት አስትዳደር፣ ስለፍትህ እና ሰላም  ይህ ነው የማይባል አስተዋጽዎ አድርጋለች ወደፊትም በሀገር ላይ መሰረታዊ እድገት እና ለውጥ ለማምጣት ተቋማቶች ቤተክርስቲያናችንን ምሰሶ አድርገው መነሳት ይኖርባቸዋል።ሌላው ክማንኛውም ሀገራችን ላይ ካለ የትምህርት ተቋም ፈርቀዳጅ በመሆን ብቻ ሳይሆን የትምህርት ሚኒስቴርም በመሆን እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ አገልግላለች።

ለዚህ ነው በዚህ ውጥንቅጡ በወጣ አለም ልጆቻቸውን ይዘው ወደ እግዚአብሄር ቤት ሲመጡ ስለ ሀይማኖታችው ብቻ ሳይሆን ስለቋንቋችው፣ሀገራቸው፣ ቅርሳቸው፣ ባህላቸው በጠቅላላ ስለ ማንነታቸው በይበልጥ እንዲያውቁ ይረዳቸዋል።

ማንነታቸውን በሚገባ የተርዱ እና ያወቁ ብሎም ሌላውን ማንነቱን እንዲያውቅ እና እንዲረዳ ይህንን ቤተክርስቲያኖችን በማቋቋም ጀምሮ በመምራት በማስተዳደር የቦርድ አባል በመሆን በማገልገል ተሳታፊ በመሆን ሌላው ወደ ቤተክርስቲያን እንዲመጣ የሚቀሰቅሱ ሁሉ በጠቅላላ የሚቀጥለው ትውልድ ማንነቱን እንዲያውቅ ጥረት የሚያድርጉ ስለሆነ እግዚአብሄር የድካማችውን ዋጋ በእጥፍ  እንዲከፍላቸው እና የመንግስቱ ወራሽ ያድርጋቸው በማለት እስናበታለሁ።

ስብሃት  ለእግዚአብሄር

Thursday, May 28, 2009

 

Mike Sutter AMERICAN-STATESMAN

The vegetarian sampler included cabbage and carrots, bottom left, red split lentils, top left, yellow split peas, center, string beans and carrots stew, right top, and collard greens.

Mike Sutter AMERICAN-STATESMAN

Spoonfuls of the vegetarian sampler of yellow split peas, red split lentils, collard greens, string beans and carrots stew, and cabbage and carrots, plus the beef chefuye and tibbs, top layers of injera.

Taste of Ethiopia

Served warm (and with warmth) in Pflugerville, a family-style education in spiced meat and vegetables


AMERICAN-STATESMAN RESTAURANT CRITIC
Wednesday, May 27, 2009

I'm no Ph.D. in gastro-culturalism, but I've seen enough to know that Ethiopian food is a full-contact sport, at least the way it's done at Taste of Ethiopia, a Pflugerville restaurant recommended to me by austin360.com colleague Matthew Odam.

The meat and vegetable dishes might come to the table in boundary-respecting bowls of their own, but unless you put a stop to it, out they go onto this flying saucer of a platter lined with injera, the Horn of Africa's answer to the tortilla or the pita.

From there, it's a free-for-all. Sweet cabbage and carrots (tikil gomen) bump into grainy yellow split peas with the peppery warmth of turmeric (ater kik), which in turn get a good soak of peppery red sauce from the rosemary-scented simmered beef (tibbs). Tear off a piece of injera and wrap it around anything that looks good, or you might get left out.

Somehow, even in these Purell-ian times, this all makes sense, propelled by the warmth of hosts Woinee Mariam and her husband, Solomon Hailu, Ethiopian immigrants who opened Taste of Ethiopia in October. The restaurant joins Aster's and Karibu in Austin as outposts for the country's love affair with garlic, red berbere spice and ginger.

For our circular bounty, we ordered the beef tibbs described above ($10.95), a sampler of five vegetarian dishes ($17.95 for two, $11.95 for one) and a beef specialty called chefuye ($11.95). Mariam spooned the dishes into two sets of roughly equal portions within the big platter, explaining the spices and components of each one as she went, saving the robust tibbs for the center. In a basket to the side, injera played a host of roles: silverware, gravy mop, napkin. It's truly a wonder bread.

In addition to the cabbage and split peas mentioned earlier, the vegetable sampler included chopped and steamed collard greens with a sly jalapeño and garlic bite (gomen), a robust stew of string beans and carrots tingling with ginger and tomato (fesolia) and aggressively spiced split lentils (yemisir wot) to keep things interesting. Brightly dressed salads of lettuce, tomato and onion took the tray's four compass points.

But the winner of the cafe-pageant sash for Most Enigmatic Dish went to chefuye, an $11.95 collection of lean beef chunks the size of robin's eggs warmed in clarified butter and served with collard greens and housemade cottage cheese. It's important to say 'warmed,' because for all practical purposes, we're talking about a fistful of raw meat. But the earthy spice warmed the mouth, and the meat was as yielding as the best tenderloin, though it came from the beef knuckle, also called the tip roast. The greens and soft cheese lent sweetness, bitterness and sour creaminess to the dish, making it a fully rounded flavor experience.

Judging from its humble home in a catch-all strip mall that includes a Mexican barbecue, a nail shop and an Asian restaurant, I didn't expect atmosphere from Taste of Ethiopia, exactly. But with muted ochre walls, a gallery-quality photo installation of Ethiopian men on horseback and a side patio tented with billowing tan fabric, the setting matched the food for its embracing warmth.

Speaking of warmth, the place gets extra-credit points for its Ethiopian coffee fortified with cardamom and cinnamon, the better to elbow out your tablemates for first dibs on the tibbs.

msutter@statesman.com; 912-5902

Taste of Ethiopia

1466 Grand Avenue Parkway, Pflugerville, 251-4053, www.tasteofethiopiaaustin.com

Rating (casual dining): 8.0 out of 10

Hours:11 a.m. to 10 p.m. daily. Lunch buffet 11 a.m. to 2 p.m. Mondays through Fridays.

Prices:Starters $3 (fried sambusas) to $5 (tomato salad). Vegetarian main courses $7.95 (split lentils in berbere-spiced sauce, called yemisir wot) to $17.95 (vegetarian sampler for two). Meat main courses $10.95 (curried beef stew called alicha siga wot) to $11.95 (berbere-spiced stew with chicken and boiled egg called doro wot). Spiced tea or Ethiopian coffee is $1.75. The lunch buffet is $8.95.

Payment:All major cards

Bar:The restaurant is just weeks away from getting its liquor license, co-owner Solomon Hailu said. After that, there will be beer and wine, including choices from Ethiopia.

Wheelchair access:Yes

What the rating means:The average of weighted scores for food, service, atmosphere and value

Saturday, May 9, 2009

 

አይሮፕላን መጣ እየገሰገሰ

በዘፈን እንደኛ ጥላሁን ገሠሠ

እሁድ ሚያዝያ 19,2009 የፋሲጋን በአል ኒውዮርክ እና ኒውጀርሲ ከቤተስቦቼ ጋር በጥሩ ሁኔታ አሳልፌ ወደ ሜሪላንድ ስለመጣሁ ሰኞ እለት ስራ የገባሁት የሞት ሞቴን ነው ሰኞ እና ሰኔ የሚያስብል ቀን ነበር ክረምቱ ወጥቶ በጋ መግቢያው ሰአት ላይ ስለሆነ ሰማዩ ልዝነብ እልዝነብ የሚል ጭቅጭቅ የያዘ ይመስላል መቼም አይደርስ የለ ከስራ መውጪያዬ ሰአት ደረሰ ያጋጣሚ ነገር ሆኖ በመስሪያ ቤቱ የምሽት ፈረቃ የሚሰራው አማርኛ ተናጋሪ ስለነበር እንደ ተለመደው ሰላምታ ከተለዋወጥን በሃላ "ሰማህ ጥላሁን ገሠሠ መሞቱን" አለኝ እኔ ደግሞ የቱ ጥላሁን ስለው "ሌላ ጥላሁን የለ ጥላሁን ገሠሠ ነዋ!!!" ወዲያውኑ ኬኔትኬት የምትኖር እህቴ ደውላ የጥላሁንን መሞት አረጋገጠችልኝ ከዛ በሃላ ቤቴ እስክደርስ ድረስ ከተለያየ ሰው ሰማሁ።

ሁላችንም ብንሆን በጥላሁን ዘፈን ይብዛም ይነስ ትዝታዎች አሉን በአብዛኞቻችን እድሜ ክልል ውስጥ ዘፈኖቹ አልፈዋል በተለይ ሙሽራዬ እና ሃይ ሎጋ ሲባል የጥላሁን የህይወቴ ህይወት የማይቀር ዘፈን ነው ሙሽራው እና ሙሽሪት ተቃቅፈው ሲያበቁ በጥላሁን ዘፈን "የህይወቴ ህይወት አንቺ በመሆንሽ እባክሽ ፍቅሬ ሆይ አልጥፋ ከፊትሽ" እያሉ ሲያዜሙ የኔስ መቼ ነው ያስብላሉ።በበኩሌ ሁሉንም የጥላሁን ዘፈን እወዳለሁ ማለት አይደለም ለምሳሌ "ዋይ ዋይ ሲሉ" የሚለውን ዘፈን በጣም ነው የምጠላው 1984 ዓ.ም. የ6ኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች እርዳታ እና ገቢ ማሰባሰቢያ በሰፊው ይካሄድ ነበር የዘፈኑ ማጀቢያ በ 1977 ዓ.ም. በድርቅ የተጎዱ ወገኖች  ቪዲዬ ነበር ታዲያ በዚህ የዘፈን ቅንብር ላይ በድርቅ ህይወታችውን ያጡ ህጻናት በጅምላ መቃብር ሲቀበሩ እና ምግብ ሲታደል ያለውን ሽሚያ የሚያሳይ ነበር። ከዛ ወዲህ ይህንን ዘፈን ቁጭ ብዬ ልሰማው ቀርቶ ያጋጣሚ የሆነ ቦታ እንኳን ተከፍቶ ስሰማ የምገባበት ነው የሚጠፋኝ።

ጥላሁን በአማካኝ ከ400 በላይ ዘፈኖችን ለሶስት ትውልዶች ተጫውቷል ይባላል። ምክንያቱን ባላውቅም ህዝብ ለህዝብ የተጫወተው "ወደፊት በሉለት ይለልይልት" የሚለው ደስይለኛል በተረፈ ዘፈኖቹ አቃቂር የሚወጣላችው አይደሉም።  ከኦሮምኛ ደግም  "ሰላማካ ያደሜ ሰላማካ" ሰምቼ አልጠግባችውም።

ለመጀመርያ ጊዜ ጥላሁንን በቅርበት የትመለከትኩት አዲስ አበባ በ1998 አ.ም. ሳር ቤት አካባቢ የሚገኘው ካልዲስ ካፍቴሪያ ውስጥ ነው። የምሰራው እዛው ህንጻ ላይ ስለሆነ ቡና እና ሻይ ለማለት አይርቀኝም የዛን እለት ልክ እንደዛሬው ቀኑ ዝናባማ ስለነበር ቡና ልበል ብዬ ወደ ካልዲስ ጠጋ ስል ጥላሁንን አየሁት ሰዎች ፊርማውን እንዲፈርምላችው በመኪናው መስኮት በኩል ሲረባረቡ ተመለክትኩኝ አይ ቡናዬን ልግዛና ሰው ትንሽ ገለል ሲል አናግረዋለው አልኩኝ ታዲያ ቡናዬን ይዤ ስመለስ ሰው የለም ጠጋ ብዬ ስጠይቅ አይ ጥላሁን ጨርሶ ሊሄድ ነው አሉኝ  ያለበት መኪና መስኮት ተዝግቶ አይስክሬሙን በማንኪያ ሲያጣጥም አየሁት ለሁለተኛ ጊዜ እና ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌደሬሽን በሰሜን አሜሪካ የብር እዩቤልዩ በሚከበርበት ጊዜ በግላጭ ተገናኘና በዊልቸር በሴት ልጁ እየተገፋ ህዝቡን ሰላምታ ሲሰጥ ነበር ያጋጣሚ ሆኖ በግላጭ ስላገኝሁት ጠጋ በማለት ጉልበቱን እና ሁለቱንም እጆች አይበሉባ ስሜ ሳበቃ ጋሽ ጥላሁን እንኳን አደረሰህ አልኩት እሱም "እግዚአብሔር ያክብርልን የኢትዩጵያ አምላክ ይጠብቃችሁ" አለ። በመቀጠልም ለማስታዎሻ አብረን ፎቶ ተነሳን ፊቱ ኮስታራ ነው ፈገግ ሲል እንኳን አላየሁትም ግርማ ሞገስ አለው ቁጭ ብሎ እንኳን ረጅም መሆኑ ያስታውቃል። በአንድ በኩል በጣም እድለኛ ነኝ ጥላሁን ገሠሠ ላይ መድረሴ ምናልባት ከዚህ በሃላ እንደሚመጣው ትውልድ ጥላሁንን በነበር ከሚያውቁት ጋር መመደብ አይቀርልኝም ነበር። የጥላሁን ገሠሠ ድንገተኛ አሟሟት አሰደንጋጭ በመሆኑ ዜናው የተለያዩ የብዙሃን መገናናን አርዕስተ ዜና ሆኖ ነበር ያለፈው ቀብር ስነ-ስርዓቱ በተፈጸመ በሳምንቱ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ማርያም ቤትክርስቲያን ላይ በተደረገው የፍትሃት ስነስርአት ላይ ተገኝቼ ነበር።ጥላሁን ገሠሠ በህይወት ባኖርም በሙዚቃዎቹ ሲታወስ ይኖራል። እግዚአብሄን ነፍሱን ይማረው ለቤተሰቡም መጽናናትን ይስጣችው።

 

       

 

Friday, May 8, 2009

 

Eating with your fingers is fun—which is just as well, because at most Ethiopian restaurants they don't give you silverware. Sometimes they don't even have silverware, so the fastidious among us have to grit their teeth, tear off a piece of injera—that fabulous Ethiopian bread made from tef or fermented millet—and sop up the marvelous tastes and textures of doro wot, lamb tibs and other fabulous concoctions.

If you're a vegetarian, there are several vegetarian options, including yellow split peas and lentils that we always include in our carnivores' dinner, but you could make a meal of them.

We also drank Ethiopian beer—and were surprised that we could get dark, medium or light. The dark was good and not too sweet and the light was also tasty. Honey wine is another good option—its sweetness perfectly complements the spicy food.

We ate at Abyssinia, our favorite Ethiopian restaurant. It's on Colfax and Albion. Try it.
 



Author: Susan Permut

Sunday, May 3, 2009

Ethiopia - Clerk slain at Denver convenience store

Police are searching for a man who fatally shot an Ethiopian immigrant inside a 7-Eleven convenience store early this morning.

The victim called police at 3:30 a.m. and told them he was shot inside the store at 567 E. Louisiana Ave. The store clerk was in an alley near the store, said Sonny Jackson, Denver police spokesman.

It is not known why he went outside, Jackson said.


denver post